ፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር
Tsehay Insurance S.C
የባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ
የስብሰባ ጥሪ
ለፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ
በኢትዮጵያ ንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 አንቀፅ 366(1)፣ 367፣ 393፣ 394 እና በኩባንያዉ መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 9 መሰረት የፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር የባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ኢትዮጵያ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ ስለሆነም የኩባንያዉ ባለአክሲዮኖች በእለቱ በቦታዉ ተገኝተዉ እንዲሳተፉ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪዉን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
የ11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች፤
-
-
- ድምፅ ቆጣሪዎችን መሰየም
- የጉባኤዉን አጀንዳዎች ማፅደቅ፤
- እ.ኤ.አ በ2021/2022 በጀት ዓመት የተሸጡ አዳዲስ አክሲዮኖችንና የአክሲዮን ዝዉዉሮችን ማሳወቅ እና አዲስ ባለአክሲዮን መቀበል፤
- እ.ኤ.አ የ2021/2022 በጀት ዓመትን የዳይሬክተሮች ቦርድ ሪፖርት መስማት፤
- እ.ኤ.አ የ2021/2022 በጀት ዓመትን የዉጭ ኦዲተሮች ሪፖርት መስማት፤
- ከላይ በተቁ.4 እና በተ.ቁ 5 በቀረቡት ሁለት ሪፖርቶች ላይ ተወያይቶ መወሰን፤
- በዘመኑ የተጣራ የትርፍ አደላደል እና አከፋፈልን በሚመለከት ተወያይቶ መወሰን፤
- የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምልመላና ምርጫ የሚያከናዉን የአስመራጭ ኮሚቴ አባላትን መምረጥ፤
- የአስመራጭ ኮሚቴ አባላት ወርሃዊ አበል ክፍያን መወሰን፤
- እ.ኤ.አ ከ2022/2023 ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ዓመታት አገልግሎት የሚሰጡ የዉጭ ኦዲተሮችን መሾም እና የ2022/2023 የአገልግሎት ክፍያቸዉን መወሰን፤
- እ.ኤ.አ የ2021/2022 በጀት ዓመት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ከተጣራ የትርፍ ድርሻ የሚታሰብ ክፍያን እና እ.ኤ.አ የ2022/2023 በጀት ዓመት ወርሃዊ አበል ክፍያን መወሰን፤
- የጉባኤዉን ቃለጉባኤ ማፅደቅ፡፡
ዋና ምዝገባ ቁጥር MT/AA/3/0017159/2004
የተከፈለ ካፒታል 292.10 ሚሊዮን
አዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 የቤት ቁጥር 2185 ስ.ቁ.0116506630/38
ማሳሰቢያ፡
-
-
- በጉባኤዉ ላይ መገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች
-
-
- በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ የተረጋገጠ እና በጉባኤዉ ላይ ለመካፈል የሚያስችል የዉክልና ስልጣን የተሰጠዉ ወኪል በእለቱ በጉባኤዉ ቦታ የዉክልና ሰነዱን ዋናዉን እና ቅጅዉን ይዞ በመገኘት በጉባኤዉ መካፈል ይችላል፡፡ ወይም
- ጉባኤዉ ከመካሄዱ ሶስት ቀናት በፊት በኩባንያዉ ዋና መስሪያ ቤት 2ኛ ፎቅ በግንባር ቀርበዉ ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀዉን የዉክልና ፎርም ሞልተዉ በመፈረም ተወካዩ ጉባኤዉን መካፈል ይችላሉ፡፡
-
-
- ባለአክሲዮኖችም ሆነ ወኪሎች ወደ ስብሰባ ቦታ ሲመጡ ማንነታቸዉን የሚገልፅ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ፤ ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ ዋናዉንና ቅጅዉን ይዘዉ መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
የፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር የዳይሬክተሮች ቦርድ
ፀሐይ ለሁሉም ታበራለች!!!